ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት ወራት ከቡና ወጪ ንግድ ከግማሽ ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

Date:

በተጠቀሰው ግዜ ከ80 ሺህ ቶን በላይ ቡና ምርት ለውጭ ገበያ በማቅረብ 546 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡

ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)፤ አርሶ አደሩ ምርቱን በቀጥታ ወደ ተለያዩ ሀገራት መላክ እንዲችል መደረጉ ለገቢው ማደግ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ብቻ ይከናወን የነበረው የቡና ጥራት ምርመራ፤ አሁን ላይ ወደ አርሶ አደሩ አቅራቢያ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

የቡና ቅምሻ ማዕከላትን በማስፋፋት፤ የተሻለ ጥራት ያላቸው የቡና ምርቶችን ወደ ዓለም ገበያ በማቅረብ የገቢ መጠኑ ማደጉን ገልፀዋል፡፡

በ2017 በጀት ዓመት 470 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 2.26 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ያስታወሱት ኃላፊው፤ በ2018 በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 3 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...