ኢትዮጵያ ባለፉት 6 ዓመታት ዓለማቀፍ የልማት ግቦችን እያሳካች እንደሆነ ተነገረ

Date:

አፈ ጉባኤው ኡዝቤኪስታን በሚካሄደው 150ኛ ዓለማቀፍ የፓርላማ ሕብረት ጉባኤ ላይ ተሳትፎ እያደረጉ ነው፡፡

አፈ ጉባኤው አገኘሁ ተሻገር በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከ2030 የዘላቂ ልማት ግቦች እና ከአፍሪካ አጀንዳ 2063 ጋር የተጣጣመ የአሥር ዓመት ሀገራዊ የልማት ዕቅድ አውጥታ እየሠራች እንደምትገኝ አብራርተዋል።

ባለፉት ስድስት ዓመታት ዓለም አቀፍ የልማት ግቦችን በማሳካት ረገድ ከፍተኛ ውጤት እያሳየች እንዲሁም ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች እንደሆነም በንግግራቸው ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፓርላማ የሚሊኒየሙን የዘላቂ ልማት ግቦች ለማሳካት የተለያዩ ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና የሕግ ማዕቀፎችን መርምሮ በማፅደቅ፣ ክትትልና ድግፍ በማድረግ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እየተወጣ ይገኛል ማለታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...