ኢትዮጵያ ባለፉት 6 ዓመታት ዓለማቀፍ የልማት ግቦችን እያሳካች እንደሆነ ተነገረ

Date:

አፈ ጉባኤው ኡዝቤኪስታን በሚካሄደው 150ኛ ዓለማቀፍ የፓርላማ ሕብረት ጉባኤ ላይ ተሳትፎ እያደረጉ ነው፡፡

አፈ ጉባኤው አገኘሁ ተሻገር በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ከ2030 የዘላቂ ልማት ግቦች እና ከአፍሪካ አጀንዳ 2063 ጋር የተጣጣመ የአሥር ዓመት ሀገራዊ የልማት ዕቅድ አውጥታ እየሠራች እንደምትገኝ አብራርተዋል።

ባለፉት ስድስት ዓመታት ዓለም አቀፍ የልማት ግቦችን በማሳካት ረገድ ከፍተኛ ውጤት እያሳየች እንዲሁም ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች እንደሆነም በንግግራቸው ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፓርላማ የሚሊኒየሙን የዘላቂ ልማት ግቦች ለማሳካት የተለያዩ ፖሊሲዎች፣ ፕሮግራሞችና የሕግ ማዕቀፎችን መርምሮ በማፅደቅ፣ ክትትልና ድግፍ በማድረግ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እየተወጣ ይገኛል ማለታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታውቋል፡፡

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...