“ኢትዮጵያ የባሕር በር አያስፈልጋትም የሚል የፖለቲካ ፓርቲ ካለ መሰረዝ ነው ያለበት”

Date:


ኢትዮጵያ የባሕር በር አያስፈልጋትም የሚል የፖለቲካ ፓርቲ ካለ ከፓርቲነት ተሰርዞ ከፖለቲካው ምዕራፍ መውጣት እንዳለበት የኢዜማ አመራርና የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ ተናገሩ።

አቶ ግርማ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ የሀገሪቱን የባሕር በር የማረጋገጥ ጉዳይ በቀጣይ ሕገ-መንግሥቱ በሚሻሻልበት ወቅት ትኩረት ተሰጥቶት የመንግሥት ግዴታ ተደርጎ ሊደነገግ ይገባል።

ለዚህም እንደ ምሳሌ ያነሱት የግብፅ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 19 የናይልን ውኃ ደኅንነት ማስጠበቅ የመንግሥት ግዴታ መሆኑን እንደሚደነግግ ጠቅሰው፣ በኢትዮጵያም የባሕር በርን ማስጠበቅ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።


ብሔራዊ ጥቅምን የማስከበር ኃላፊነት በመንግሥት ላይ መጣል እንዳለበት የገለጹት አቶ ግርማ፤ ከዚህ ብሔራዊ ጥቅም በተቃራኒ የሚቆሙ አካላትን መቆጣጠር የመንግሥት ግዴታ ሊሆን እንደሚገባም አመልክተዋል።

የባሕር በር ጥያቄ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ባለፈ የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑንና ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ለዚህ ግብ መሳካት ቅድሚያ መስጠት እንዳለበትም በአጽንኦት ገልጸዋል።

ጋዜጣ_ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...