የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተመዝግበው ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) እና ከአሜሪካ መንግስት ሌሎች ተቋማት የገንዘብ ድጋፍ በመቀበል በአገሪቱ ውስጥ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ሲያከናውኑ የነበሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መረጃቸውን ለሚመለከተው የመንግስት አካል እንዲያቀርቡ ተጠየቁ።
ይህ ጥሪ የአሜሪካ አስተዳደር በአገር ውስጥም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ እያደረገ ያለውን የገንዘብ ድጋፍ መቀነስ ወይም ማቆም ጋር በተያያዘ ለቀጣይ ተግባራት አስፈላጊውን መረጃ ለመሰብሰብ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ ስለሆነም USAIDን ጨምሮ ከማንኛውም የአሜሪካ መንግስት ተቋም የገንዘብ ድጋፍ ሲያገኙ የነበሩ ሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እስከ ሚያዝያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ለሚመለከተው ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣነሰ ሪፖርት እንዲያደርጉ በጥብቅ ማሳሰቢያ መስጠቱ ለማወቅ ተችሏል።
CapitalNews
