ከአሜሪካ የተባረሩት የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር የጀግና አቀባበል ተደረገላቸው

Date:

“ምርጫችን ባይሆንም ወደ ቤት በመመለሳችን ግን አንጸጸትም።…እንደዚህ ዓይነት አቀባበል ሲደረግልን በደቡብ አፍሪካ ነጮች ላይ የዘር ማጥፋት አለ የሚሉ ውሸቶችን ውድቅ እንዳደረግን በወደድን ነበር፤ ነገር ግን በአሜሪካ ይህን ለማሳካት አልቻልንም” ሲሉ ኬፕ ታውን ሲደርሱ በደጋፊዎቻቸው ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው አምባሳደር ኢብራሂም ራሱል ተናግረዋል።

“በመጋቢት ወር አጋማሽ ከአሜሪካ እንዲወጡ የተነገራቸው ዲፕሎማቱ፤ ደቡብ አፍሪካ ከአሜሪካ ጋር ከ50 ዓመት በላይ ያስቆጠረ ግንኙነቷን ‘ማስተካከልና እንደገና መገንባት’ እንዳለባት ተናግረዋል። ግንኙነቱ መጠገን ያለበት ግን ‘የደቡብ አፍሪካን እሴቶች አሳልፎ በመስጠት’ እንዳልሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል።

“ፍልስጤማውያንን መስዋዕት ማድረግ የለብንም። ብሪክስን አንተውም። ከቻይና ጋር ያለንን ግንኙነት አናቆምም። ከአሜሪካ ጋር ያለንን አጋርነትም አንተውም። መታገል ይኖርብናል፤ ክብራችንን ግን መጠበቅ አለብን” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...