ወጣቷ ድምፃዊት ሀና ግርማ ከ አንድ አመት ቆይታ በኃላ አዲስ ነጠላ ሙዚቃ ይዛ እየመጣች ችገኛለች፡፡የሙዚቃው መጠርያ “ሃዬ”ይሰኛል በግጥም አሜጢቆ በዜማ አቡዲ ከቅንብር እስከ ማስተሪንግ ታምሩ አማረ(ቶሚ) የሙዚቃው ዳሬክተር ሌንጮ ፍቅሩ ከውነውታል፡፡
የኢትዮጲያን አይዶል ትሩፋት የሆነችው ወጣቷ ድምፃዊት ሀና ግርማ ከዚህ ቀደም የተለያዩ ነጠላ ሙዚቃዎችን አድርሳናለች፡፡በጥቂቱ ለመግለፅ ያህል በመጀመሪያ በለቀቀችው”ጨረቃ” ነጠላ ዜማዋ አድናቆትን ተችራለች።
በመቀጠልም”ከተሜ”፣”ባንተ-ላይ”፣”ምን መሠለህ” የሙዚቃ ስራዎቿ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከአንድ አመት ጊዜያት በኃላ “ሃዬ” ብላ በአዲስ ነጠላ ሙዚቃ መጥታለች በናሆም ሪከርድስ በኩል አርብ ምሽት ይለቀቃል፡፡ይጠብቁት፡፡
via፡ ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ(ሐጌ ኢቨንት)
