ከ1ሺህ በላይ ተፅእኖ ፈጣሪ የስራ ሀሳቦች በመረጃ ቋት ዉስጥ እንደተመዘገቡ ተገለፀ

Date:

የስራ ሀሳቦቹን ወደ ተግባር ቀይሮ ለመቀጠል ግን የሀገር ዉስጥ ባለሀብቱ ፍላጎት እያሳየ አይደለም ተብሏል።

በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ስር የሀሳብ ባንክ በተባለ የምዝገባ ስርአት ዉስጥ አዳዲስ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሀሳቦችን መመዝገቡን ሰምተናል።

ሆኖም በመረጃ ቋቱ ያሉትን ሀሳቦች መሬት ለማዉረድ ክፍተቶች አሉ ተብሏል።

የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ስምሪት እና ገበያ ዘርፍ ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በሀገርአቀፍ ደረጃ ተወዳድረዉ ያሸነፉ ብቁ የስራ ፈጠራዎች የጎረቤት ሀገራት ባለሀብቶች ተመርጠዉ ወደ ቢዝነስ እየተቀየሩ መሆኑን ገልፀዋል።

በሀገር አቀፍ ዉድድሮች ችግር ፈቺነታቸዉ ታምኖበት የተመረጡ ሀሳቦችን የግል ዘርፉን እገዛ የሚጠይቅ እየሆነ ነዉ ተብሏል።

የሚኒስትር መስሪያ በቤቱ በተለይም ለክልሎች ለአዳዲስ የስራ ፈጠራ ሃሳቦች መሰረታዊ ድጋፍ እንዲረግ እየጠየቀ ነዉ የሚሉት ሚኒስትር ዴኤታዉ ሆኖም በባለሀብቱም በኩል ይህንን እያገዘ አይደለም ብለዋል።

አሁንም የክህሎት ልማት ዉድድር እያከናወነ ነዉ የሚሉት አቶ ሰለሞን ሶካ የቴክኖሎጂ መፍትሔ ያላቸዉ ሀሳቦችን እይታ እንዲኖራቸው ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ ገልፀዋል።

የስራ ፈጠራ ውድድሮች ከውጤታማነት እና ቀጣይነት አኳያ ውስንነቶች እንዳሉባቸው ይነሳል።

በተለያዩ አካላት የሚዘጋጁ የስራ ፈጠራ ውድድሮች እየተበራከቱ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን ከውጤታማነት እና ቀጣይነት አኳያ ሲታዩ ግን ከፍተኛ ውስንነት እንዳለባቸው በተደጋጋሚ ይገለፃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...