የስራ ሀሳቦቹን ወደ ተግባር ቀይሮ ለመቀጠል ግን የሀገር ዉስጥ ባለሀብቱ ፍላጎት እያሳየ አይደለም ተብሏል።
በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ስር የሀሳብ ባንክ በተባለ የምዝገባ ስርአት ዉስጥ አዳዲስ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሀሳቦችን መመዝገቡን ሰምተናል።
ሆኖም በመረጃ ቋቱ ያሉትን ሀሳቦች መሬት ለማዉረድ ክፍተቶች አሉ ተብሏል።
የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የስራ ስምሪት እና ገበያ ዘርፍ ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በሀገርአቀፍ ደረጃ ተወዳድረዉ ያሸነፉ ብቁ የስራ ፈጠራዎች የጎረቤት ሀገራት ባለሀብቶች ተመርጠዉ ወደ ቢዝነስ እየተቀየሩ መሆኑን ገልፀዋል።
በሀገር አቀፍ ዉድድሮች ችግር ፈቺነታቸዉ ታምኖበት የተመረጡ ሀሳቦችን የግል ዘርፉን እገዛ የሚጠይቅ እየሆነ ነዉ ተብሏል።
የሚኒስትር መስሪያ በቤቱ በተለይም ለክልሎች ለአዳዲስ የስራ ፈጠራ ሃሳቦች መሰረታዊ ድጋፍ እንዲረግ እየጠየቀ ነዉ የሚሉት ሚኒስትር ዴኤታዉ ሆኖም በባለሀብቱም በኩል ይህንን እያገዘ አይደለም ብለዋል።
አሁንም የክህሎት ልማት ዉድድር እያከናወነ ነዉ የሚሉት አቶ ሰለሞን ሶካ የቴክኖሎጂ መፍትሔ ያላቸዉ ሀሳቦችን እይታ እንዲኖራቸው ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ ገልፀዋል።
የስራ ፈጠራ ውድድሮች ከውጤታማነት እና ቀጣይነት አኳያ ውስንነቶች እንዳሉባቸው ይነሳል።
በተለያዩ አካላት የሚዘጋጁ የስራ ፈጠራ ውድድሮች እየተበራከቱ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን ከውጤታማነት እና ቀጣይነት አኳያ ሲታዩ ግን ከፍተኛ ውስንነት እንዳለባቸው በተደጋጋሚ ይገለፃል።
