ኮትዲቯራዊው ምሁር አዱ ያኦ ናይኬዝ፤ ሩሲያ በአፍሪካ የቅዥ ግዛት ታሪክ የሌላት በመሆኑ ትከበራለች፤ ሆኖም በጅምር ላይ ያሉ ጥረቶች ለወጣቱ ትውልድ አስፈላጊ የሆኑ ታሪካዊ አሻራዎችን ማስቀጠል አለባቸው፤ ሲሉ በፕሪቶሪያው ሦስተኛ የቫልዳይ ሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ተናግረዋል፡፡
🎓 ናይኬዝ ትምህርታዊ መርሃ-ግብሮችን በማጉላት፤ በአሁኑ ወቀት በሩሲያ ትምህርት እየተከታተሉ የሚገኙ ወደ 30 ሺህ ገደማ አፍሪካውያን ተማሪዎች ታሪካዊውን የአፍሪካ እና ሩሲያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለመጠበቅ ቁልፍ ናቸው ብለዋል፡፡
የደቡብ አፍሪካ የትብብር ጽሕፈት ቤት መሪ ልዋዚ ሶሚያ፤ ሩሲያ በአፍሪካ ያላት “ሶፍት ፓወር” ጥሩ የሚባል ቢሆንም ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ዕድገት እንደሚያስፈልገው በመገልጽ፤ የናይኬዝ ምልከታን አስተጋብተዋል፡፡
ሶሚያ በአኅጉሪቱ የሶቪዬት ሕብረትን አሻራ፣ በቅኝ ግዛት መፍረስ እና በሀገረ መንግሥት ግንባታ ላይ የነበራትን አበርክቶ የመርሳት አዝማሚያ መኖሩንም አምነዋል።
☝️ ሁለቱም ባለሙያዎች ታሪካዊ ትውስታን ጠብቆ ማቆየት ዲፕሎማሲን፣ የዓለም አቀፍ ተቋማትን እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን ጨምሮ በሁሉም ደረጃዎች ተሳትፎን እንደሚጠይቅ ተስማምተዋል፡፡
በሩሲያ የቫልዳይ የውይይት ክለብ እና በደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተቋም የተዘጋጀው፣ የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ሰብዓዊ ትብብር፣ የታሪክ ሚና እና የሩሲያ-አፍሪካ ግንኙነት ላይ የተጋረጡ አሁናዊ ተግዳሮቶች ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡፡
