የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

Date:

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር ሊሰሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓትን ለማስተካከል የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን ለአምባሳደሩ አብራርተውላቸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየተወሰዱ ያሉ ሪፎርሞችና የተያዙ ራዕዮችን እንገነዘባለን ያሉ ሲሆን በቀጣይ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይቶች ለትምህርት ዘርፉ የሚደረጉ ድጋፎች ለታለመላቸው አላማ ይውሉ ዘንድ ከመተግበራቸው አስቀድሞ መወያየት እንደሚያስፈልግም ተስማምተዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...