Home Uncategorized የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር ሊሰሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓትን ለማስተካከል የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን ለአምባሳደሩ አብራርተውላቸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየተወሰዱ ያሉ ሪፎርሞችና የተያዙ ራዕዮችን እንገነዘባለን ያሉ ሲሆን በቀጣይ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይቶች ለትምህርት ዘርፉ የሚደረጉ ድጋፎች ለታለመላቸው አላማ ይውሉ ዘንድ ከመተግበራቸው አስቀድሞ መወያየት እንደሚያስፈልግም ተስማምተዋል፡፡