የነጻነት ወርቅነህን ሕጋዊ የቤተሰብ ተወካይን ስለ ማሳወቅ

Date:

በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ሕልፈት ምክንያት ሐዘናችንን ሐዘናችሁ በማድረግ ላፅናናችሁን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። የአርቲስት ነፃነት ቤተሰብ ወደመጡበት ሃገር ከመመለሳቸው በፊት ለቤተሰቡ የቅርብ ሰዎች ሕጋዊ ውክልና ሰጥተዋል ።

በመሆኑም ፣ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህን የተመለከቱ ማናቸውንም የሥራ ጉዳዮች እንዲከታተሉና እንዲያስፈጽሙልን በማለት አቶ አስናቀ ንጉሴን የወከልን መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን።

ከአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ስም ጋር በተያያዘ ማንኛውም ጉዳይ ቢኖራችሁ አቶ አስናቀ ንጉሴን ማነጋገር እንደምትችሉ እንገልፃለን።

ከዚህ በተጨማሪም ፣ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ እና ቤተሰቡን የተመለከተ የትኛውንም ዓይነት መረጃ ማግኘት ስትፈልጉ ተወካዩን በአካል ወይም በስልክ ማነጋገር ትችላላችሁ። በተለይ የሟችንም ሆነ የቤተሰቡን ስም የሚያጠፉ እንዲሁም ክብር የሚያጎድፉ ስሁት ትርክቶችን በማህበራዊ ሚዲያ እንዳይዘዋወሩ ለማስቀረት እንዲቻል ፣ ትክክለኛ መረጃዎችን ከሕጋዊ ተወካያችን ብቻ እንዲቀበሉ ፤ የተወካያችንን ቃል ብቻ ጠቅሰው እንዲጠቀሙ እንጠይቃለን።

ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ የሟችንም ሆነ የቤተሰቡን መልካም ስም የሚያጎድፍ ስሁት የፈጠራ ታሪክ ማሰራጨት በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑንም እናስታውሳለን።

ስልክ :- 0903886870 ( አስናቀ ንጉሴ )

ቤተሰቡ

SHARE በማድረግ መልዕክቱን እንድታዳርሱልን እንጠይቃለን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...