የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን እንደገለፀው ፤ ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ በአፍሪካ የሚገኙ የአሜሪካ ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮዎች እንቅስቃሴን ለመቀነስ ዝግጅት ስለመደረጉ ያወጣው መረጃ ትክክለኛ አይደለም ብሏል።
ጋዜጣው በትላንትናው እትሙ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱን ለማዋቀር የሚያስችል አስፈፃሚ ትዕዛዝ በማዘጋጀት ላይ መሆናቸውን የሚገልፅ ጽሑፍ አስነብቧል።
@sputnik_ethiopia
