የኢራንን ጦርነት ተቃውመው ከሥልጣናቸው የለቀቁት የአሜሪካ ብሔራዊ የፀረ ሽብር ማዕከል የቀድሞ ዳይሬክተር ጆ ኬንት፤ በኤፍቢአይ ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሆነ ተገለጸ።
ምርመራው ምሥጢራዊ መረጃዎችን ለተለያዩ ምንጮች አሹልከዋል በሚል የተከፈተ እንደሆነ በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ለጉዳዩ ቅርበው ያላቸውን ምንጮችን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባ ያሳያል።
በኤፍቢአይ የወንጀል ክፍል የተያዘው ይህ ምርመራ ባለሥልጣኑ ከኃላፊነት ከመልቀቃቸው አስቀድሞ የተጀመረ እና ለተወሰነ ጊዜ ሲካሄድ የቆየ መሆኑን ምንጮች ተናግረዋል ተብሏል።
የቀድሞው የፀረ ሽብር ኃላፊ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከኃላፊነታቸው የለቀቁት ኢራን “ምንም ድርስ አደጋ” አልደቀነችም እንዲሁም “ጦርነቱ የተጀመረው በእስራኤል እና ጉልበት ባላቸው የአሜሪካ የውትትወታ ተቋማት ግፊት ነው” በሚል ነበር።
ረቡዕ ዕለት ከወግ አጥባቂው የፖለቲካ አስተያት ሰጪ ታከር ካርልሰን ጋር በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ፤ የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተቃውመዋል። ኻሜኒን መግደል አሜሪካ ልትወስድ ከምትችላቸው እርምጃዎች መካከል “የመጨረሻ” መሆን እንደነበረበት ተናግረዋል።
“የኒውክሌር ፕሮግራማቸውን እያለዘበ ነበር፤ የኒውክሌር መሳሪያ እንዳያገኙ እየተከላከላቸው ነበር” ብለዋል።
