የኢትዮጵያን የሎጂስቲክ ዘርፍ እድገት  አንድ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ የእዉቅና መድረክ

Date:

የፊያታ አለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር ከፍተኛ ዲፕሎማ የአሰልጣኞች ስልጠና የማጠቃለያ መርሐግብር ማከናወኑን አስታወቀ። 

በመርሃግብሩ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ ሚኒስትር ዶክተር አለሙ ስሜን ጨምሮ በርካታ የሃገር ዉስጥ እና አለም አቀፍ የሎጂስቲክ ባለሙያዎች ታድመዉበታል።

በተለያዩ የሙያ መስኮች ለተሰማሩ አርባ የሎጂስቲክ ባለሙያዎች ለአስራ አምስት ቀናት በፊያታ አለምአቀፋ ከፍተኛ ባለሙያ አማካኝነት የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል። 

ሰልጠናዉ የኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ዘርፍ የሠዉ ሀይል ልማት ላይ የራሱን አሻራ እንደሚያሳርፍ እና የኢትዮጵያ የሎጂስቲክ ዘርፍ አንድ እርምጃ እንደሚያራምድ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ የእቃ አስተላፊዎችና የመረከብ ወኪሎች ማህበር ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ የሎጂስቲክ ዘርፍ በማዘመን ለአገሪቱ የምጣኔ ሃብት እድገት ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን በሎጂስቲክ ዘርፍ የሚታየውን ክፍተት ለመሙላት በርካታ እንቅስቃሴዎችን እንደሚያደርግም ተገልጿል።

NBC Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...