የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በጅቡቲ ተሸለመ

Date:

የጅቡቲ ትራንዚተርስ አሶሴሽን የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ (ኢባትሎ) በሎጂስቲክስ ዘርፍ ላበረከተው ዓይነተኛ አስተዋጽኦ እና አጋርነት ሽልማት ማበርከቱ ተነግሯል ።

ትናንት በጅቡቲ አምባሳደሮችና የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በተደረገው የዕውቅና አሰጣጥ ፕሮግራም ላይ ማህበሩ ላለፉት ዓመታት በነበረን የአብሮነት ጉዞ በስራ አጋርነት ላሳያችሁት ድንቅ ብቃትና ዘላቂ ወዳጅነት ለኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ያለንን ክብር እንገልፃለን ሲል ሸልማቱን መስጠቱን ነዉ የተገለጸው ።

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ክቡር በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ባለን የጋራ ስራ የጭነት ምጣኔን ከፍታ በማረጋገጥና ገቢያችንን በማሳደግ፣ ግንኙነታችንን በማጠናከር፣ የስራ ፈጠራን በማስፋት፣ የሰራተኞቻችንን ጤናማነት በማረጋገጥ ለጠንካራ የኢኮኖሚ ግንባታ መረጋገጥ እና የሁለትዮሽ ተጠቃሚነት እናውለዋለን ብለዋል፡፡

ይህ ሽልማት የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ድርጅት በክልሉ የሎጂስቲክስ ዘርፍ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ የሚያሳይ ሲሆን፣ የሁለቱ አገራት የትብብር ግንኙነት ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ይጠበቃል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...