የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በጅቡቲ ተሸለመ

Date:

የጅቡቲ ትራንዚተርስ አሶሴሽን የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ (ኢባትሎ) በሎጂስቲክስ ዘርፍ ላበረከተው ዓይነተኛ አስተዋጽኦ እና አጋርነት ሽልማት ማበርከቱ ተነግሯል ።

ትናንት በጅቡቲ አምባሳደሮችና የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በተደረገው የዕውቅና አሰጣጥ ፕሮግራም ላይ ማህበሩ ላለፉት ዓመታት በነበረን የአብሮነት ጉዞ በስራ አጋርነት ላሳያችሁት ድንቅ ብቃትና ዘላቂ ወዳጅነት ለኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ያለንን ክብር እንገልፃለን ሲል ሸልማቱን መስጠቱን ነዉ የተገለጸው ።

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ክቡር በሪሶ አመሎ (ዶ/ር) እንደተናገሩት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ባለን የጋራ ስራ የጭነት ምጣኔን ከፍታ በማረጋገጥና ገቢያችንን በማሳደግ፣ ግንኙነታችንን በማጠናከር፣ የስራ ፈጠራን በማስፋት፣ የሰራተኞቻችንን ጤናማነት በማረጋገጥ ለጠንካራ የኢኮኖሚ ግንባታ መረጋገጥ እና የሁለትዮሽ ተጠቃሚነት እናውለዋለን ብለዋል፡፡

ይህ ሽልማት የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ድርጅት በክልሉ የሎጂስቲክስ ዘርፍ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ የሚያሳይ ሲሆን፣ የሁለቱ አገራት የትብብር ግንኙነት ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ይጠበቃል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...