ትራምፕ እንዳስታወቁት ከቬንዚዌላ ነዳጅ በመግዛት ወደ ሃገሩ በሚያስገባ ማንኛውም ሃገር ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል ብለዋል፡፡
ትራምፕ በትሩዝ ማህበራዊ ድረገጻቸው ላይ በጻፉት መልዕክት ቬንዚዌላ ከአሜሪካ ጋር እጅግ ጠበኛ ሃገር ነች ስለዚህም ከቬንዚዌላ ላይ ነዳጅ የሚገዙ ሃገራት ከአሜሪካ ጋር በሚኖራቸው የንግድ ልውውጦች ላይ 25 በመቶ ታሪፍ ይጣልባቸዋል ይህም ከ ሚያዚያ 12 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡
ስፔን ህንድ ሩሲያ ሲንጋፑር እና ቬተናም ከ ቬንዚዌላ ላይ ነዳጅ በመግዛት ከሚታወቁት ውስጥ ናቸው፡፡
እስከ ዛሬ ባለው ራሷ አሜሪካም ከቬንዚዌላ ነዳጅ ስታስገባ የቆየች ሲሆን ባለፈው ጥር ወር ብቻ 8 ነጥብ 6 ሚሊየን በርሜል ነዳጅ ከቬንዚዌላ አስገብታለች፡፡
ባጠቃላይ ከጥር ወር ወዲህ ሁለት መቶ ሁለት ሚሊየን በርሜል ነዳጅ አሜሪካ ከሃገሪቱ ገዝታለች ሲል የዘገበው ዩሮ ኒውስ ነው፡፡
