ዶናልድ ትራምፕ ከቬንዚዌላ ነዳጅ በሚገዙ ሃገራ ላይ የ 25 በመቶ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ

Date:

ትራምፕ እንዳስታወቁት ከቬንዚዌላ ነዳጅ በመግዛት ወደ ሃገሩ በሚያስገባ ማንኛውም ሃገር ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል ብለዋል፡፡

ትራምፕ በትሩዝ ማህበራዊ ድረገጻቸው ላይ በጻፉት መልዕክት ቬንዚዌላ ከአሜሪካ ጋር እጅግ ጠበኛ ሃገር ነች ስለዚህም ከቬንዚዌላ ላይ ነዳጅ የሚገዙ ሃገራት ከአሜሪካ ጋር በሚኖራቸው የንግድ ልውውጦች ላይ 25 በመቶ ታሪፍ ይጣልባቸዋል ይህም ከ ሚያዚያ 12 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡

ስፔን ህንድ ሩሲያ ሲንጋፑር እና ቬተናም ከ ቬንዚዌላ ላይ ነዳጅ በመግዛት ከሚታወቁት ውስጥ ናቸው፡፡

እስከ ዛሬ ባለው ራሷ አሜሪካም ከቬንዚዌላ ነዳጅ ስታስገባ የቆየች ሲሆን ባለፈው ጥር ወር ብቻ 8 ነጥብ 6 ሚሊየን በርሜል ነዳጅ ከቬንዚዌላ አስገብታለች፡፡

ባጠቃላይ ከጥር ወር ወዲህ ሁለት መቶ ሁለት ሚሊየን በርሜል ነዳጅ አሜሪካ ከሃገሪቱ ገዝታለች ሲል የዘገበው ዩሮ ኒውስ ነው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...