ግብፅ በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ አትገኝም

Date:

የኢትዮጵያ መንግስት የህዳሴውን ግድብ  እንዲጎበኙና በምርቃት ስነስርአቱም ላይ  እንዲገኙ ጥሪ እንዳቀረበላቸው የገለጹት የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ፤ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ እንደማይገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ አስታውቀዋል፡፡

‹‹ግብዣው ምንም ዓይነት ፖለቲካዊም ሆነ ህጋዊ አመክንዮ የለውም›› ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግብፅ ለምርቃቱ እንደማትገኝና ተወካዮችንም  እንደማትልክ ገልጸዋል፡፡

ሚኒስትሩ “አል ሾሩክ” ከተሰኘው የግብፅ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ አገራቸው ብሄራዊ የውሀ ደህንነቷን ማስነካት እንደማትፈቅድ አስረግጠው  ተናግረዋል፡፡

‹‹የአባይ ውሀ ለድርድር ወይንም ለንግግር የሚቀርብ ሳይሆን ከመላው የግብፅ ህዝብ ጋር የተያያዘ የህልውና ጉዳይ ነው›› ብለዋል፤ ከጋዜጣው ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፡፡

ባድር አብደላቲ አክለውም፤ ‹‹የግብፅን ስትራቴጂካዊ ጥቅምና የአባይ ውሀ ታሪካዊ ድርሻችንን የሚጎዳ ግድብን እንድንጎበኝ ግብዣ ማቅረብ ተገቢ ነውን?›› ሲሉም  ጠይቀዋል፡፡

ባድር አብደላቲ አክለውም፤ ‹‹ስለ ግብዣው ማውራት ትርጉም የለሽና በምንም ስሌት የማይሆን ነው›› ብለዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...