ግብፅ በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ አትገኝም

Date:

የኢትዮጵያ መንግስት የህዳሴውን ግድብ  እንዲጎበኙና በምርቃት ስነስርአቱም ላይ  እንዲገኙ ጥሪ እንዳቀረበላቸው የገለጹት የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ፤ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ እንደማይገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ አስታውቀዋል፡፡

‹‹ግብዣው ምንም ዓይነት ፖለቲካዊም ሆነ ህጋዊ አመክንዮ የለውም›› ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግብፅ ለምርቃቱ እንደማትገኝና ተወካዮችንም  እንደማትልክ ገልጸዋል፡፡

ሚኒስትሩ “አል ሾሩክ” ከተሰኘው የግብፅ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ አገራቸው ብሄራዊ የውሀ ደህንነቷን ማስነካት እንደማትፈቅድ አስረግጠው  ተናግረዋል፡፡

‹‹የአባይ ውሀ ለድርድር ወይንም ለንግግር የሚቀርብ ሳይሆን ከመላው የግብፅ ህዝብ ጋር የተያያዘ የህልውና ጉዳይ ነው›› ብለዋል፤ ከጋዜጣው ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፡፡

ባድር አብደላቲ አክለውም፤ ‹‹የግብፅን ስትራቴጂካዊ ጥቅምና የአባይ ውሀ ታሪካዊ ድርሻችንን የሚጎዳ ግድብን እንድንጎበኝ ግብዣ ማቅረብ ተገቢ ነውን?›› ሲሉም  ጠይቀዋል፡፡

ባድር አብደላቲ አክለውም፤ ‹‹ስለ ግብዣው ማውራት ትርጉም የለሽና በምንም ስሌት የማይሆን ነው›› ብለዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...