የትግራይ ተፈናቃዮች በሚገኙበት የሱዳን አምራኩባ የመጠለያ ጣብያ ባጋጠመ የእሳት አደጋ ቃጠሎ አደጋ የ6 ዓመት ህፃን ህይወት ወዲያው ተቀጥፏል።
ሌላ የሁለት ዓመት ህፃን በደረሰበት ጉዳት ለተጨማሪ ህክምና ተልኳል።

የእሳት ቃጠሎው ላለፉት ሦስት ዓመታት መደጋገሙ አደጋውን እጅግ አሳሳቢ አድርጎታል ተብሏል። TMH
መጠለያው በሚገኝበት አከባቢ በቂ የህክምና እና የመድሃኒት አቅርቦት ባለመኖሩ ምክንያት አደጋውን የመከላከል ስራ አዳጋች አንደሆነ ተፈናቃዮችን ዋቢ በማድረግ ቲኤምኤች እና ድምጺ ወያነ ዘግበዋል።
