ሩስያ ሁለት የዩክሬይን መንደሮችን ተቆጣጠረች

Date:

የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲንና የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በአላስካ ውይይት ባደረጉበት ከሰዓታት ቆይታ በኋላ ሩስያ ሁለት የዩክሬይን መንደሮችን መቆጣጠሯን አስታውቃለች።

የሩስያ የመከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ በዶኔስክ ዞን የምትገኘውን ኮሎዲያዚ እና በዲፕሮቴትሮቭስክ ዞን የምትገኘውን የቮሩን ከተሞችን መቆጣጠሩን አስታውቋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ከዩክሬይን መንግስት በኩል ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የተሰጠ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም።

በሌላ ዜና ዩክሬይን ሩስያ በምትቆጣጠረው የኩርሱክ ግዛት ባካሄደችው የድሮን ጥቃት አንድ አባትና ልጅ መገደላቸውን ሩስያ አስታውቃለች።

የአካባቢው አስተዳዳሪን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው አባትና ልጅ የሞቱት በመኪና በሚጓዙበት ጊዜ በደረሰባቸው የድሮን ጥቃት ነው።

መኪናው በዩክሬይን ድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙን ነው አስተዳዳሪው የገለጹት ሲሉ የዘገቡት አዣንስ ፍራንስ ፕረስና ሮይተርስ ናቸው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...