የሱዳን ጦር አዛዥ አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ከ2013ቱ መፈንቅለ መንግሥት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀድሞ የተባበሩት መንግሥታት ዲፕሎማትና የፕሬዝዳንት እጩ ካሚል ኢድሪስን ጠቅላይ ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል።
ሹመቱ ዲፕሎማቱን ዳፋላህ አል-ሃጅ አሊን ጊዜያዊ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርጎ ለመሾም የተደረገው ሙከራ ሳይሳካ በመቅረቱ የመጣ ነው።
አል ቡርሃን በተጨማሪም ሰልማ አብደል ጀባር አልሙባራክን በድጋሚ የሾሙ ሲሆን ኖዋራ አቦ ሞሐመድ ሞሐመድ ታሂርን ደግሞ ወደ ሉዓላዊ ምክር ቤቱ አክለዋል።
የሱዳን ጦር በመጋቢት ወር ካርቱምን ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ነፃ ማውጣቱ የሚታወስ ነው።
