በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሀያ ሰባተኛ ሳምንት ጨዋታ የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች በመባል የአርሰናሉ አጥቂ ቪክቶር ዮኬሬሽ መመረጡ ይፋ ተደርጓል። በዚህም መሰረት የአርሰናሉ የፊት መስመር አጥቂ ቪክቶር ዮኬሬሽ የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ተብሏል
የ 27 አመቱ የመድፈኞቹ አጥቂ ቪክቶር ዮኬሬሽ በለንደን ደርቢ ጨዋታ አርሰናል ቶተንሀምን ባሸነፈበት ጨዋታ ሁለት ምርጥ ጎሎችን ማስቆጠሩን ተከትሎ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ በይፋ ተመርጧል።
የቀድሞ የአርሰናል ተጫዋች የነበረዉ ኢያን ራይት “ቪክቶር አሁን ከቡደኑ ወሳኝ ተጫዋች ዉስጥ አንዱ ለመሆን ሁሉም ነገር አለዉ በጥሩ ሰአት ወደ ብቃቱ መመለሱ ለአርቴታ ደስታን የሚፈጥር ነዉ” ሲል ራይት አስተያየቱን ሰቷል።
