በመሬት መንቀጥቀጥ ስጋት ከመተሀራ አካባቢ የተነሱ ከ32 ሺሕ በላይ ዜጎች ወደ ቀያቸው እንደሚመለሱ ተገለጸአካባቢው ተመሳሳይ አደጋ እንደማያስከትል በጥናት ተረጋግጧል ተብልዋል

Date:

በአዋሽ ፈንታሌ በተከሰተው ርዕደ መሬት ምክንያት አደጋ እንዳይደርስባቸው በመስጋት መተሃራ አካባቢ ባሉ 7 ቀበሌዎች የሚኖሩ ከ32 ሺሕ 620 ነዋሪዎች አካባቢውን እንዲለቁ ተደርጎ እንደነበር፤ የኦሮሚያ ክልል ቡሳ ጎኖፋ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ኃላፊ ጥበቡ ኩምሳ ለአሐዱ ተናግረዋል።  

በአሁን ሰዓት በአካባቢዎቹ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ስጋት ባለመኖሩ ምክንያት ነዋሪዎቹን ወደቀደመ መኖሪያ አካባቢያቸው የመመለስ ሥራ መጀመሩን አብራርተዋል።

ኃላፊው በተጨማሪም፤ “ተፈናቃዮቹ ከአካባቢያቸው ከተነሱ በኋላ ባሉት ሦስት ወራት የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ባለመኖሩ ነዋሪዎቹ ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ ተደርጓል” ብለዋል።

በአዋሽ ፈንታሌ መተሃራ ከተፈናቀሉት ከ32 ሺሕ 620 ሰዎች በተጨማሪ የመሬት መንቀጥቀጡ ጉዳት እንደማያደርስባቸው በመስጋት ተፈናቅለው በአፋር ክልል የሚገኙ ከ60 ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች የሚገኙ ሲሆን፤ ተፋናቃዮቹ አሁን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡

#አሐዱ ሬድዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...