▪️ ሁለት የተኩስ አቁም ስምምነት አማራጮች ቀርበዋል።
▪️ የመጀመሪያው አማራጭ የዩክሬን ጦር በዶንዬትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ፣ በሉሃንስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ፣ ዛፖሮዢያ እና ሄርሶን ክልሎች ከያዟቸው የሩሲያ ግዛቶች መውጣትን ያካትታል።
▪️ ሁለተኛው አማራጭ የወታደሮች ስምሪትን ማስቆም፣ ምልመላ እና ለኪዬቭ የሚደረገውን የውጭ ወታደራዊ ዕርዳታ ማቆም፣ ወታደሮችን መበተን እና የሶስተኛ ሀገራት ወታደራዊ ተሳትፎን ማስቀረት የተመለከቱ አንቀጾችን ያካትታል።
▪️ ሰነዱ የዩክሬን ገለልተኝነትን እና ወታደራዊ ጥምረቶችን ለመቀላቀል ያላትን ውጥን መተው እንዳለባት ይገልጻል።
▪️ በዩክሬን የሌሎች ሀገራትን ወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚከለክል አንቀጽ ተካቷል።
▪️ ዩክሬን ከኒውክሌር ነጻ መሆን እንዳለባትና የዩክሬን ሠራዊት ሊኖረው ስለሚገባ የመጨረሻ ቁጥር ያስቀምጣል።
▪️ በሩሲያ ላይ የተጣሉት የኢኮኖሚ ማዕቀቦችን ማንሳት።
▪️ ክራይሚያ፣ ዶኔዬትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ዛፖሮዥዬ እና ሄርሰን ክልሎች የሩሲያ ግዛቶች ስለመሆናቸው ዓለም አቀፍ እውቅና መስጠት።
▪️ በወታደራዊ እርምጃ ከደርሰው ጉዳት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎችን በጋራ ስምምነት ማንሳት።
▪️ የሩሲያኛ ተናጋሪ ሕዝብ መብቶችን እና ነጻነቶችን ማረጋገጥ፣ በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴዎች ላይ የተጣሉትን ገደቦች ማንሳት እና ናዚዝምን ውድቅ ማድረግ።
