በአርቲስት ጥላሁን ጉግሳ የተመሠረተው የቤት ስራ ማህበር የመሰረት ድንጋይ አስቀመጠ

Date:

ሀምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም፣ (ሀገሬ ቴቪ)፤ ‎በአርቲስት ጥላሁን ጉግሳ እና ወጣት ሀብታሙ አሰፋ መስራችነት የተቋቋመው ህብረት አምባ የቤቶች ማህበር ለሚያስገነባው የመኖርያ ቤቶች የመሰረት ድንጋይ በዛሬው እለት አስቀምጧል።

‎ማህበሩ ዛሬ የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጠው በጫካ ሲቲ አቅራብያ በሚገኘው 6ሺ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ሲሆን በቀጣይነትም ባሉት ከ20ሺ ካሬ ሜትር በሆነ ቦታ ላይ የመኖርያ ቤቶች ግንባታ እንደሚያከናውን አስታውቋል።

ማህበሩ ለግንባታ የሚጠቀማቸው ቦታዎች ቀድሞውኑ የማህበሩ ይዞታዎች ‎እስካሁን ከ150 በላይ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን በቀጣይም በሺዎች የሚቆጠሩ መኖርያ ቤቶችን ገንብቶ ለነዋሪዎች የማስተላለፍ እቅድ ያለው መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው እለት የመሠረት ድንጋይ የተጣለለት የጋራ መኖርያ ቤት ህንፃ በሶስት አመት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ ለባለቤቶቹ እንደሚተላለፍ ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...