ቤልጅየም እ.ኤ.አ ከ2025/2026 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሞባይል ስልኮችን እና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን መጠቀም እንደማይቻል አስታውቃለች።
የጤና እክል ወይም ድንገተኛ አደጋዎች ካልተፈጠሩ በስተቀር የሞባይል ስልኮች በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚታገዱ የቤልጅየም የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
እገዳው በሁሉም ክልሎች ተግባራዊ ይሆናል የተባለ ሲሆን፤ ስልክ ይዘው በተገኙ ላይ ትምህርት ቤቶች ራሳቸው የዲሲፕሊን ርምጃዎችን እንደሚወስኑ ተገልጿል።
በብራስልስም በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሞባይል ስልኮችን መጠቀም ካለፈው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ሲሆን፤ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ደግሞ አጠቃቀምን ለመከላከል ጥብቅ ገደቦችን አውጥተዋል ሲል አናዶሉ ዘግቧል።
