ኢራን በጎረቤት ሀገራት ላይ ጥቃት አለመሰንዘሯን አስታወቀች

Date:

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኢል ባጋሃይ፤ ሀገራቸው በቱርክ፣ በቆጵሮስ እና በአዘርባጃን ላይ ጥቃት ፈጽማለች ተብሎ የሚናፈሰውን መረጃ አስተባበሉ።

ባለፈው ሳምንት ተፈጽመዋል የተባሉትን ጥቃቶች አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ከኢራን ግዛት የተሰነዘረ ምንም ዓይነት ጥቃት አለመኖሩን አረጋግጠዋል።

ቃል አቀባዩ አክለውም፤ ጥቃቶቹ በኢራን እና በጎረቤት ሀገራት መካከል ቅራኔ ለመፍጠር በ“ጠላት” የተደራጁ ሴራዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

በአሁኑ ወቅት ስለ ተኩስ ማቆም ድርድር የሚነሱ ሃሳቦችን ውድቅ ያደረጉት ባጋሃይ፤ ወታደራዊ ግጭቶች ባልቆሙበት ሁኔታ ስለ ሸምግልና ማውራት “አስፈላጊ አይደለም” ብለዋል። “ይህ ጦርነት በእኛ ላይ የተጫነ እንጂ እኛ የጀመርነው አይደለም” ሲሉ የገለጹት ቃል አቀባዩ፤ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱ ቀዳሚ ትኩረት ሉዓላዊነትን ማስጠበቅ ላይ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...