ኢትዮ ቴሌኮም፣ ከኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጋር ዘመናዊ የዲጂታል ጤና አቅርቦት ሰንሰለት ሶሉሽን ለመተግበር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
ይህ ትብብር የመድኃኒት እና የህክምና ቁሳቁሶች ስርጭትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማቀላጠፍ አሰራሩን የበለጠ አስተማማኝ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል።
ስምምነቱ የአቅርቦት ሰንሰለቱን በ AI-የታገዘ የደህንነት ስርዓት፣ በስማርት ቪዲዮ ትንተና፣ በዘመናዊ የቁጥጥር ክፍሎች እና በኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያ በማሻሻል ፈጣን እና በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ለማድረግ ያግዛል።
ዛሬ መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተፈረመው ይህ ስምምነት የስራ ጫናን መቀነስ፣ የመድኃኒት ቁጥጥርን ማሻሻል፣ እና የእቃ ክምችት ስርዓት ትክክለኛነትን ማሳደግን ጨምሮ በርካታ አዎንታዊ ውጤቶችን ያስገኛል ተብሎ ይጠበቃል።
