የእግር ኳሱ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ2025 ከ275 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማግኘት የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ መሆን ችሏል።
ለሳዑዲዉ ክለብ አልናስር እየተጫወተ የሚገኘው ሮናልዶ ከስፖንሰር ሺፕ እና ከደሞዝ ጥቅማጥቅሞች ያገኘው ገቢ ከዓለም ቀዳሚው ስፖርተኛ አድርጎታል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ ሲሆን ይህ ለ3 ተከታታይ ዓመታት መሆኑን ፎርብስ ዘግቧል።
የቅርጫት ኳሱ ኮከብ ስቴፈን ከሪ በ 156 ሚሊዮን ዶላር ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፤ ብሪታንያዊው ቦክሰኛ ታይሰን ፉሪ በ146 ሚሊዮን ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
ሌላኛው የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ 135 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 5ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡
እንዲሁም ሌላኛው የእግር ኳስ ተጫዋቾች ካሪም ቤንዜማ 104 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 8ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ተጫዋች ሆኗል።
