“የበርበሬ ዐውሎ ነፋስ” በድምቀት ተመረቀ

Date:

በደራሲ አበረ ሽፈራው የተፃፈው “የበርበሬ ዐውሎ ነፋስ” የተሰኝው አዲስ መፅሐፍ ዋልያ መጽሐፍት አዳራሽ በርካታ ታዳሚያን በተገኙበት በድምቀት ተመረቀ ::


በዚህ የመጽሐፍ ምርቃት ፕሮግራም ላይ ሰለሞን ሳህለ፣ ቢንያም ውብሸት ፣ ኤደን ሃብታሙ ፣ እናኑ ግርማ ፣ ህይወት እምሻው ከመጽሐፉ ላይ በንባብ እቅቅርበዋል:: ደራሲ አበረ ሽፈራው በአዲስ ልሳን ጋዜጣ እና በፉና በጋዜጠኝነት አገልግሏል::

የእለቱ የክብር እንግዳ በመሆን መጽሐፉን በይፋ የመረቁት የመጽሐፉ ደራሲ አበረ ሽፈራው ወላጅ አባት እና የአበረ የትዳር አጋር የሆነችው የደራሲ ህይውት እምሻው እናት ነበሩ:: የደራሲው ወላጅ አባት በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ እንደተናገሩት :-

” ከልጅነቱ ጀምሮ መጽሐፍ ማንበብብ ይወድ ስለነበር እኔም በወር እስከ ሶስት መጵሐፍትን እየገዛሁ እንዲያነብ አደርግ ነበር::
ዛሬ እርሱም መጽሐፍ ጽፎ የእርሱን መጽሐፍ ለመመረቅ ስለበቃሁ በጣም ደስ ብሎኛል::


እንክዋ ደስ ያለህ ” በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል::ደራሲውም ለአባቱ የአክብሮትና የምስጋና ሥጦታ አበርክቷል::

(ይትባረክ ዋለልኝ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...