ኢብራሂም ትራኦሬ “ነጻ፣ ባለ ብዙ ዋልታ፣ ሰዎች ነጻ፣ ሉዓላዊ እና የፈለጉትን የሚሆኑበት ዓለም በመፍጠር ረገድ ተመሳሳይ አመለካከት አለን” ብለዋል።
የቡርኪናፋሶው ፕሬዝዳንት ዛሬ ከሩሲያው አቻቸው ፑቲን ጋር ይወያያሉ ።
ሁለቱ መሪዎች የቡርኪናፋሶ ወጣቶችን ማሰልጠን ጨምሮ በትምህርት ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ።
የፑቲን እና ትራኦሬ የዛሬ ምሽት ውይይት “መከላከያ፣ ትምህርት እና የባለብዙ ዋልታ ዓለም” ላይ እንደሚያተኩር የቡርኪናፋሶው መሪ ገልጸዋል ።
ኢብራሂም ትራኦሬ ሲያብራሩ “ብዙ ጎበዝ እና ብልህ፣ በሳይንስ ጥሩ የሆኑ ቡርኪናፋሶያውያንን ማሰልጠን ያስፈልጋል። ሀገሪቱን ማሳድግ የሚቻለው በሳይንስ ነው” ብለዋል ሲል ስፑትኒክ አፍሪካ ዘግቧል።
