የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የአፍሪካንዊያንን የመልማት ህልም ዳግም ከፍ ያደረገ ነው

Date:

የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር  በአራት ዋና ዋና ጉዳዮች  ዙሪያ በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው የታላቁ  የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነበራት  ዲፕሎማሲያዊ  ግንኙትት ላይ ተጨማሪ ግብዓት ሆኗታልም ሲሉ  ሰፋ ያለ ማብራሪያ አድርገዋል።

የግድቡ መጠናቀቅ ከኢትዮጵያውን አልፎ ለአፍሪካዊያን አዳዲስ የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን በአለም አቀፍ ደረጃ  የእድል በር  የከፈተ አጋጣሚ  ተገኝቶበታል ብለዋል።

በዚሁ መግለጫ በአዲስ አበባ የተካሄደው የአፍሪካ  የአየር ንብረት ጉባዔ ላይ ማብራሪያ የሰጡት ቃል አቀባዩ ከ25 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች መገኘታቸውን ገልፀዋል። በጉባዔው የኢትዮጵያን ጥቅም የሚያስከብሩ ሰነዶች ተካተዋልም ተብሏል።

በጉባዔው መጨረሻም የአፍሪካ የአየር ንብረት ፈንድ እንዲቋቋምም ከስምምነት መደረሱን የውጭ ጉዳይ መግለጫ አስታውቋል።

የአፍሪካ ካረቢያን ማህበረሰብ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄዱን ያስታወሱት ቃል አቀባዩ፤ በዚሁ ጉባዔ አዳዲስ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደተመሠረተም ተጠቁሟል።

በተለይም ባርባዶስ ከኢትዮጵያ ጋር የስራ እድል ለዜጎች ለመስጠት ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር መስማማታቸው  ተመላክቷል።

የአፍሪካ ካረቢያን ጉባዔ ተሳታፊዎች የታላቁ ህዳሴ ግድብ መመረቁ ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካ አርአያነቷን ያስመሠከረችበት ነው ማለታቸው ተገልጿል።

በመጨረሻም በቀጣዩ ሳምንት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) 80ኛ ጉባዔውን በኒውዮርክ እንደሚካሄድ ተጠቁሟል።  

በዚሁ ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን የሚያስከብሩ አጀንዳዎችን ይዛ ተሳታፊ እንደምትሆን አምባሳደር ነብያት ይፋ አድርገዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...