ልክ በዛሬዋ ቀን ሰኔ 5 1956ዓ.ም የፀረ አፓርታይድ ታጋዩ እና የደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ፓርቲ መሪው ኔልሰን ማዴላ የዕድሜ ልክ እስራት የተበየነባቸው ቀን ነበር፡፡
በአገር ክህደት ወንጀል እና በህገወጥ መንገድ ከአገር ለመውጣት በመሞከር በተደጋጋሚ በሮበን ደሴት እስር ቤት ሲታሰሩ ሲፈቱ የነበረ ሲሆን በኋላም አሻጥር ፈፅመዋል በሚል ኔልሰን ማንዴላ የዕድሜ ልክ እስራት ተበየነባቸው።
ማንዴላ ጠባብ በሆነች ክፍል ያለማረፊያ ከከባድ የጉልበት ስራ ቅጣት ጋር ሲሰቃዩ ኖረው መጨረሻ ላይ አገራቸውን ከአፓርታይድ አገዛዝ ነፃ አውጥተው ፕሬዝዳንት እስከመሆንም ደርሰዋል፡፡
በዚህ ድርጊታቸውም የሰላም ኖቤል ተሸላሚ የሆኑ አፍሪካዊ መሪ ሆነው ነበር።
ማንዴላ በጥቂት ነጮች የበላይነት የተያዘውን የመንግስት እና የዘር መድሎን በመቃወም ከህጋዊ ሰላማዊ የፓርቲ ትግል እስከ የደፈጣ ትግል በማድረግ ያሰቡትን ዓላማ አሳክተዋል፡፡
የፀረ አፓርታይድ ታጋዩ እና የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ፓርቲ መሪው ኔልሰን ማዴላ በ95 አመታቸው እ.ኤ.አ በታህሳስ 5 2013 በደቡብ አፍሪካ አርፈዋል።
