ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን በፕሬዝዳንትነት ለመምራት ብቁ የሚሆኑ ዕጩዎችን እንዲጠቆሙ ለክልሉ ህዝብ ጥሪ አቀረቡ። ዕጩዎቹ “የጊዜያዊ አስተዳደሩን ስራዎች በብቃት የሚያከናውኑ” እንዲሁም “የክልሉን ሰላም እና ደህንነት ማረጋገጥ የሚችሉ መሆን” ይገባቸዋል ተብሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ጥሪ ያቀረቡት፤ ለመላው የትግራይ ህዝብ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት መልዕክት ነው። በትግርኛ ቋንቋ የተጻፈው የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት፤ “የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጥቆማ ጥሪ” በሚል ርዕስ የቀረበ ነው።
