የአዕምሮ ህመም (ሳይኮሲስ) ጥናት መካሄድ ጀመረ

Date:

በአገራችን የተመረጡ ክልሎች እና አዲስ አበባ ላይ ጥናቱ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአዕምሮ ህክምና ትምህርት ክፍል ስር የሚገኘው እስኮፕ ፕሮጀክት ጥናቱን የሚያከናውን ይሆናል።

በጥናቱ የአዕምሮ ህመሙ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታዎችን በማጥናት የተሻለ የህክምና አገልግሎት ተደራሽነት፣ የታማሚዎችን እና ቤተሰቦቻቸውን ጤና እና ኑሮ በማሻሻል ምርምር እንደሚደረግ ተገልጿል።

በጥናቱ የሚሳተፉት የአዕምሮ ህሙማን እና ቤተሰቦቻቸው ከማህበረሰቡ ውስጥ የሚመረጡ እንደሆነም ተነስቷል።

ጥናቱ ፅኑ የአዕምሮ ህመም ያለባቸውን ሰዎች በመለየት በቶሎ እርዳታ እንዲያገኙ እና የተሻለ ህይወት መምራት እንዲችሉ የሚያደርግ ነው ተብሏል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በኦሮሚያ በተመረጡ ወረዳዎች እና በአዲስአበባ ቂርቆስ እና ልደታ ክፍለከተሞች ላይ ጥናቱ ይካሄዳል።

እነዚህ ቦታዎች የተመረጡበት ምንም የተለየ ምክንያት እንደሌለም ተገልጿል።

ለ25 አመታት በአሁኑ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተለይ ቡታጅራ ላይ ስለ አዕምሮ ጤና ሲሰራ ቆይቷል ሲሉ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶክተር ውብዓለም ክልሉ የተመረጠበትን ምክንያት አብራርተዋል።

ኦሮሚያ ክልል ላይም ባለው የፀጥታ ሁኔታ ተደራሽ መሆን የሚቻልባቸው ቦታዎች ላይ ጥናቱ እንደሚደረግ አንስተዋል።

ቂርቆስ እና ልደታ ክፍለከተሞችም የተመረጡት የበለጠ ተጋላጭነት ስላለባቸው ሳይሆን ፤ እነዚህ ቦታዎች ላይ በመስራት ቀሪውን ለመንግስት ለመስጠት በመታሰቡ ነው ብለዋል።

ጥናቱ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...