የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ “ጥላ” ተብለው በሚጠሩትና እስካሁን በቂ ቁጥጥር በማይደረግባቸው የፋይናንስ ተቋማት ላይ አዲስ የቁጥጥር መመሪያ ሊያወጣ መሆኑን ገለጸ።
በዚህም መሠረት እስካሁን በኅብረት ሥራ ኮሚሽን ስር ሲመሩ የነበሩት የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት እና በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሚያንቀሳቅሱት የጡረታ ፈንዶች በብሔራዊ ባንክ ቀጥተኛ ቁጥጥር ስር የሚውሉ ይሆናል።
የዚህ እርምጃ ዋና ዓላማ በፋይናንስ ዘርፉ ያለውን ያልተገባ የገበያ ውድድር ለማስቀረት መሆኑን ካፒታል ለመረዳት ችሏል።
