የወንጂ ከረሜላ ፋብሪካ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት የጥራት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ማግኘቱ ተገለፀ።
የወንጂ/ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የ2018 በጀት ዓመት የሰባት ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ በተካሄደበት ወቅት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢዩኤል ለላንጎ ፋብሪካው የጥራት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማግኘቱ የምርት ጥራትና ተወዳዳሪነት ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
ፋብሪካው ከ14 ዓመታት በኋላ በይፋ መከፈቱ ሲበሰር አሁን ባለው አቅም በዘጠኝ አይነት ጣዕም በዓመት እስከ 2 ሺህ 400 ቶን ከረሜላ የማምረት አቅም እንዳለው መገለፁ ይታወሳል።
