ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ስምምነት አደረገ

Date:

የዳንጎቴ ቡድን በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት የ3 ቢሊየን ዶላር ስትራቴጂካዊ ስምምነት ማድረጉን የቡድኑ ፕሬዝዳንት እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ አስታወቁ፡፡

ፕሬዝዳንቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የማዳበሪያ ፋብሪካ በሶማሌ ክልል ጎዴ ለመገንባት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የ3 ቢሊየን ዶላር ስትራቴጂካዊ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል፡፡

ይህ ፕሮጀክት ኢንቨስትመንት ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያ በግብርና ዘርፍ ራሷን እንድትችል እና ቀጣናዊ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለመፍጠር ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፤ የአቅርቦት ችግር ያለባቸውና ከሞሮኮ እና ሩሲያ በሚመጡ ምርቶች ላይ ጥገኛ የሆኑ ሀገራት አፋጣኝ ርምጃ መውሰድ አለባቸው።

ዓላማችን የዩሪያ እና የናይትሮጅን ማዳበሪያዎችን በሀገር ውስጥ በማምረት የኢትዮጵያን ገበሬዎችን ፍላጎት ለማሟላት እና በመላው ምሥራቅ አፍሪካ እየተመዘገበ ያለውን ዕድገት ማበረታታት ነው ብለዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ራዕይ እና ሀገር በቀል ኢኮኖሚያዊ ሪፎርም መሰረት ስትራቴጂካዊ ስፍራ በሆነው የኢትዮ – ጅቡቲ ድንበር ላይ የምትገኘው የጎዴ ከተማ አዲስ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንደምትሆንም አመላክተዋል፡፡

በኢትዮጵያ በሲሚንቶ ዘርፍ ያገኘነውን ስኬት ተከትሎ ይህ አዲስ ተነሳሽነት በምሥራቅ አፍሪካ ለምናደርገው መስፋፋት ወሳኝ ርምጃ ነውም ሲሉም በጽሁፋቸው ገልጸዋል፡፡

አክለውም አፍሪካ ራሷን መመገብ አለባት። በጋራ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ የስራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የመጭውን ትውልድ መፃኢ ዕድል እንገነባለን ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...