ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ ሶስት ዋና ዋና አላማዎችን ይዞ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ከእነዚህም ድህነትን መቀነስ ሴቶችን በኢኮኖሚ ማጎልበት እና ትምህርት ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል ።
ድህነትን ለመቀነስ ትምህርት ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት ያስፈልጋል ሲሉ የሪች ፎር ቼንጅ ካንትሪ ማናጀር የሆኑት መቅድም ጉልላት በተለይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። አክለውም በተለያዩ መንገድ ዌብሳይት ቀርሰው ለሚሰሩ እና የመማር ማስተማር ሂደቱን በበዙ መንገድ እየረዱ ላሉ እና ለሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ የፈተና ልምምድ ጊዜ እንዲወስዱ እና ወጤታማ ትውልድ ለመፍጠር እየሰሩ ይገኛሉ።
የገንዘብ እጥረት ለሚያጋጥማቸው እስከ 60 ሺህ ዶላር ድጋፍ እንደሚደርግላቸው ተጠቁሟል። በተጨማሪም ሪች ፎር ቼንጅ ኢትዮጵያ ከስዊድን ጋር ለ80 ዓመታት የዘለቀው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን የሚያጠናክር መሆኑን በዕለቱ ዝግጅት የተገኙት የስዊድን ባለስልጣናት በስራቸው ላሉ ተቋማት የስራ ሂደት እና ውጤት ተመልክተዋል።
በአሁኑ ወቅት ሪች ፎር ቼንጅ ትምህርት አጋዥ መተግበርያዎችን እና መፍትሄዎችን የፈጠሩ ወጣት ሶሻል ኢንተርፕረነሮችን አቅማቸውን የማጎልበት የገበያ ትስስር በመፍጠር እና የገንዘብ ደጋፍ በማድረግ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ይገኛል::
ሪች ፎር ቼንጅ ለትርፍ ያልተቋቋመ ዓለምአቀፋዊ ግብረ ሰናይ ደርጅት ሲሆን በዋናነትም በማህበረሰብ ወስጥ የሚስተዋሉ ችግሮቸን ለመፍታት የተለሙ ሥራ ፈጣሪዎችን የሚያግዝ ግብረሰናይ ድርጅት ነዉ::
