“ ጨዋታው የሚደረገው ህዳሴ መመረቂያ ላይ በመሆኑ ትልቅ ትርጉም አለው “ አቶ ባህሩ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አርብ ከግብፅ ጋር ያለበትን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ አስመልክቶ በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን “ ጨዋታው ልዩ ትኩረት የሰጠነው ነው “ ሲሉ ገልጸዋል።

“ ጨዋታው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን እንዲሁም የኢትዮጵያ ህዝብም ትልቅ ትርጉም የሚሰጠው ጨዋታ ነው “ ሲሉ አቶ ባህሩ ጥላሁን ተናግረዋል።

አክለውም “ ጨዋታው ትልቅ ታሪካዊ አሻራችንን ያስቀመጥንበት ህዳሴ ግድብ በሚመረቅበት እና ንጋት ሀይቅ በተሰየመበት ሰዓት ስለሆነ የሚደረገው ትልቅ ትኩረት ሰጥተነዋል “ ብለዋል።

“ ቡድኑ የተቻለውን ሁሉ እንዲያደርግ እንፈልጋለን ያንን እንዲያደርግም ነው ቀደም ብሎ ዝግጅት እንዲጀምር ያደረግነው “ አቶ ባህሩ ጥላሁን

የዋልያዎቹ ዋና አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ በበኩላቸው “ ጠንካራ ጨዋታ ነው የሚጠብቀን “ ብለዋል።

“ እኛም በዛው ልክ ተገቢውን ጥሩ ዝግጅት አድርገናል ሜዳ ላይ የሚሆነውን እናያለን “ ሲሉ አሰልጣኙ ተናግረዋል።

@tikvahethsport    

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...