ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወሳኙን የኢራን የነዳጅ ማስተላለፊያ ደሴትን በቅርቡ እንደሚቆጣጠሩ አስታወቁ

Date:

የኢራን እና የአሜሪካ ግጭት ከዕለት ወደ ዕለትእየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ወቅት ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዛሬም በድጋሚ በኢራን ላይ ከባድ ጥቃት እንደሚፈጸም እና በቅርቡም አሜሪካየኻርግ ደሴትን እንደምትቆጣጠር አስታወቁ።ፕሬ

ዝዳንቱ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩ“ባሕር ኃይሏ፣ የአየር ኃይሏ፣ የአየር መከላከያ ሥርዓቷ እና ሁሉም የጥቃት አቅሟ” ወድሟል ያሏት ኢራንን ዳግም ዛሬ “ሌሊትበኃይለኛው ትመታለች” ብለዋል። “ቬን

ዙዌላ ላይ እንዳደረግነው ብዙም ሳይቆይየኻርግ ደሴትን እና ሌሎች የነዳጅ መሠረተ ልማቶችን እንይዛለን፤ በዚህም የኢራንን የነዳጅ እና የጋዝ ገበያን ሙሉ ለሙሉ እንቆጣጠራለን”ሲሉ ዕቅዳቸውን አሳውቀዋል።  ከኢራ

ን ጋር የሚደረገው ጦርነት ከተጀመረበት ጊዜአንስቶ ፕሬዝዳንት ትራምፕ የኢራን ዋነኛው የነዳጅ ማስተላለፊያ የሆነውን ኻርግ ደሴትን እንደሚቆጣጠሩ በተደጋጋሚ ሲናገሩ ነበር።በሰሜና

ዊ የባሕረ ሰላጤው አካባቢ የሚገኘው ኻርግደሴት ኢራን ወደ 90 በመቶ የሚሆነውን የነዳጅ ምርቷን ለቀሪው ዓለም የምታቀርብበትት ዋና መተላለፊያ ነው።ደሴቱ ከ

ኢራን የባሕር ዳርቻ አቅራቢያ የሚገኝሲሆን፣ ወደ ሁለት ሚሊዮን በርሜል መጫን የሚችሉ ግዙፍ ድፍድፍ ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ ነዳጅ ለመሙላት የሚያስችል ጥልቅየውሃ ክፍል አለው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...