የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በሶስት ከፍተኛ የጦር አዛዦች ላይ ጊዜያዊ እገዳ ጥለዋል።
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ በትግራይ የጸጥታ ሃይሎች ከፍተኛ አዛዦች በኃይል ስልጣን ለመንጠቅ የሚደረገውም እንቅስቃሴ በመገምገም ውሳኔ አሳልፏል ።
ፕሬዝደንት ጌታቸው እንደተናገሩት ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከታች እግሩን እንዳይረግጥ የሚከላከልበት መንገድ አሁን የትግራይን የጸጥታ ሃይሎች ጭምር በመጠቀም ስልጣን ለመያዝ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ማህተሞች እስከ መንጠቅ ተደርሷል ብሏል።
ከፍተኛ የጸጥታ ሃይሎች እንቅስቃሴውን እንዲያቆሙ ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ ያሳሰቡ ሲሆን እንቅስቃሴው የሰራዊቱን አንድነት የሚያናጋ ሁኔታ እየፈጠረ ነውም ብለዋል። በዚህም ለጊዜው የታገዱት ሜጀር ጄኔራል ዮሃንስ ወልደጊዮርጊስ፣ ሜ/ጄኔራል ማሾ በየነ እና
ሌ/ጄኔራል ምግብይ ሀይሌ ዋና አዛዦች መሆናቸውን ትግራይ ቴሌቪዢን ያሰራጨው የጊዜያዊ አስተዳደሩ ደብዳቤ ያሳያል ።
