49 ሰዎችን አሳፍሮ የነበረ የሩሲያ አዉሮፕላን ተከሰከሰ

Date:


43 መንገደኞችንና 6 ሠራተኞችን አሳፍሮ ይበር የነበረ አንድ የሩሲያ የመንገደኞች አዉሮፕላን ሩሲያን ከቻይና ጋር በሚያውስነዉ ድንበር አካባቢ ተከሰከሰ።

አንቶኖቭ 24 (A-24) የተባለዉ አዉሮፕላን  ዛሬ ጧት ሩሲያን ከቻይና ጋር ከሚያዋስነዉ ድንበር ላይ ከምትገኘዉ ብላጎቬሽሼንስክ ከተባለችዉ ከተማ ትይንዳ ወደተባለች ሌላ ከተማ መብረር ላይ ነበር።

አዉሮፕላኑ አሳፍሯቸዉ ከነበሩት ሰዎች በሕይወት የተረፈ መኖሩ ብዙ አጠራጥሯል።አዉሮፕላኑ በወደቀበት አካባቢ ቀድመዉ የደረሱ የአደጋ ሠራተኞች በእሳት የተቃጠለ የአዉሮፕላኑን ሥብርባሪ ማግኘታቸዉን አስታዉቀዋል።

አዉሮፕላኑ ይበር በነበረበት አካባቢ «አስቸጋሪ» የዓየር ሁኔታ ነበር ከመባሉ በስተቀር የአደጋዉ ትክክለኛ መንስኤ አልታወቀም።


(ፎቶ፣-የተከሰከሰዉ አዉሮፕላን ዓይነት፣ A-24)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...