የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን እና እስራኤል መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረሱን ገለፁ።
ሁለቱ አገራት ግን በይፋ የተኩስ አቁም ስለመደረሱ ያሉት ነገር የለም።
ኢራን እስራኤል የምትፈጽመውን ጥቃት የምታቆም ከሆነ እርሷም ሚሳዔሎችን ማስወንጨፍ እንደምታቆም ተናግራለች።
ትናንት ምሽት ኢራን በኳታር ወደሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ሚሳዔሎችን አስወንጭፋ ነበር።
ይህ ከሆነ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው ትራምፕ በኢራን እና እስራኤል መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረሱን በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ያሳወቁት።
ትራምፕ ሁለቱም አገራት በ24 ሰዓታት ውስጥ ጥቃት መፈጸማቸውን ያቆማሉ ብለዋል።
ነገር ግን ከዚያ በኋላም እስራኤል በኢራን የሚገኙ ዒላማዎች ላይ ድብደባ መፈፀሟ ተሰምቷል።
እስራኤል ሁለቱ አገራት በቀጣዮቹ 24 ሰዓታት ውስጥ ተኩስ ያቆማሉ ለሚለው የትራምፕ መግለጫ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠችም።
