የኩርዱ ታጣቂ ቡድን የቱርክን ግጭት ለማስቆም ወሰነ

Date:

 

ከ 40 አመታት የትጥቅ ትግል በኋላ በቱርክ መንግስት ህገ-ወጥ ተብሎ የተፈረጀው የኩርድ ፒ.ኬ.ኬ የጦር መሳሪያ የማስረከብ የመጀመሪያ እርምጃን ለማሳየት ዛሬ አርብ ሥነ-ስርዓት አካሂዷል።

ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት በኢራቅ ኩርዲስታን የሚጀመር ሲሆን በበጋውም ወቅት በሙሉ ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል። የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እርምጃውን “በሀገራችን እግር ላይ የተጣሉትን ደም አፋሳሽ ሰንሰለት ሙሉ በሙሉ ነቅሎ መጣል ነው” ሲሉ አድንቀዋል።

ግጭቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ 40 ሺ ያህል ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ፒኬኬ በቱርክ፣ ዩናይትድ ስቴትስ፣ አውሮፓ ህብረት እና እንግሊዝ ውስጥ በአሸባሪ ቡድንነት ተመዝግቧል።

ትጥቅ ማስፈታቱ ሂደት በቱርክ ብቻም ሳይሆን በኢራቅ፣ ሶሪያ እና ኢራን ውስጥ ይተገበራል።ጥቂት የፒኬኬ አባላት ወደ ሰፈራቸው ከመሄዳቸው በፊት በሱለይማንያህ በኢራቅ ኩርዲስታን በተካሄደ ሥነ ሥርዓት መሣሪያቸውን በተምሳሌታዊ በተባለ ሁኔታ አስቀምጠዋል።

የቱርክ ደጋፊ የኩርድ ተቃዋሚ ዴም ፓርቲ አባላት ሂደቱን እየተከታተሉ ሲሆን የቱርክ ሚዲያዎችም ዘግበዋል። የቱርክ፣ የኢራቅ እና የኩርዲስታን ክልላዊ መንግስታት በሚያሳትፉበት ቦታ በሚቀጥሉት ወራት ትጥቅ ማስፈታቱ እንደሚቀጥል ይጠበቃል።

ለረጅም ጊዜ በእስር ላይ የሚገኙት የፒኬኬ መሪ አብዱላህ ኦካላን “ከትጥቅ ትግል ምዕራፍ ወደ ዲሞክራሲያዊ ፖለቲካ እና ህግ በፈቃደኝነት የተደረገ ሽግግር ነው” ብለዋል።

እ.ኤ.አ. በ1999 ከተያዘቡት ጊዜ አንስቶ ከኢስታንቡል በስተደቡብ ምእራብ በምትገኘው ኢምራሊ በምትባል ትንሽ እስር ቤት ውስጥ ለብቻቸው ታስረው ይገኛሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...