ኢትዮጵያ አየር መንገድ በመቀሌ ምን ገጠመዉ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET-298 በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ተነስቶ መቀሌ አሉላ አባነጋ አየር ማረፊያ ካረፈ በኋላ ከአውሮፕላን መንደርደሪያው መጠነኛ የመንሸራተት እክል አጋጥሞታል። አውሮፕላኑ በሚያርፍበት ጊዜ ዝናብ እየዘነበ ነበር።

እስካሁን ባለን መረጃ በክቡራን መንገደኞቻችን ላይ ምንም አይነት ጉዳት ያልደረሰና በሰላም ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ የተደረገ ሲሆን በሁለት የበረራ ሰራተኞቻችን ላይ መጠነኛ ጉዳት በማጋጠሙ ለተጨማሪ የህክምና ዕርዳታ በአቅራቢያ ወደሚገኝ የህክምና መስጫ ተቋም ተወስደው ከታከሙ በኋላ ወደ ሆቴል እንዲሄዱ ተደርገዋል።

ምንግዜም ለደንበኞች ደህንነት ቅድሚያ የሚሰጠው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው የደንበኞች መጉላላት ይቅርታ እየጠየቀ ተጨማሪ መረጃ ሲኖር ለክቡራን ደንበኞቹ የሚያሳውቅ መሆኑን በአክብሮት ይገልፃል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...