አድማስ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች በሚሊኒየም አዳራሽ አስመርቋል።
በምረቃ ሥነሥርዓቱ ለይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቱው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሞላ ፀጋዬ ፤ ዩኒቨርስቲው ባለፉት 26ዓመታት በመደበኛና በርቀት ትምህርት በድግሪ ፣በዲፕሎማና በሰርተፍኬት በርካታ ተማሪዎችን በማሰልጠን ማስመረቁን ተናግረዋል ።
ዩኒቨርሲቲው በሃገሪቱ የልማት እንቅስቃሴ ውስጥ የሚፈለገው የተማረ የሰው ሃይል አሰልጥኖ በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል ።
በዛሬው እለት ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ያስመረቀው አድማስ ዩኒቨርሲቲ ካስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል 71 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል ።
አድማስ ዩኒቨርስቲ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በሶማሌላንድና ፑንትላንድ ቅርንጫፍ ከፍቶ እያስተማረ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።
ተመራቂ ተማሪዎች በሠለጠኑበት የሞያ መስክ ሀገራቸውንና ህዝባቸውን በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል ።
