ሁለተኛው ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያን ይግዙ የንግድ ሳምንት ኤክስፖ ነሀሴ 24 እንደሚጀመር የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) እንደገለጹት የንግድ ሳምንቱ ከነሀሴ 24 እስከ ነሀሴ 29/2017 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ጥራት መንደር ይካሄዳል።
በንግድ ሳምንቱ የኢትዮጵያ ምርቶች የሚቀርቡበትና የሚተዋወቁበት የኢትዮጵያን ይግዙ ኤግዚቢሽንና ባዛር እንደሚኖር ጠቁመው ይህም የገበያ ትስስር ለመፍጠር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል።
እንደ ጋዜጣ ፕሬስ ዘገባ በሀገራዊ የንግድና የቢዝነስ አጀንዳዎች ላይ የፓናል ውይይት ይካሄዳል።
በንግድ ሳምንቱ 168 የንግድ ድርጅቶች፣ የቢዝነስ አጋሮችና ክልሎች እንደሚሳታፉ ይጠበቃል ።
