ዩክሬን ተዋጊ ጀት ገዛች

Date:


የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ አንድ መቶ የጦር ጀቶችን ለመግዛት መፈራረማቸው ተገለፀ ።

የጦር መሳሪያ ፍለጋ ወደ ፈረንሳይ ያቀኑት ዘለንስኪ ፣ ከፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ለቀጣይ አስር ዓመት የጦር መሳሪያ ስምምነት አድርገዋል ።

የዘለንስኪ ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፣ ፈረንሳይ እና ዩክሬን ፣ ፓሪስ አጠገብ በሚገኘው ቪላኮብላይ የአየር ማዘዣ ላይ ዓላማ ተኮር አዋጅ (declaration of intent) የተሰኘ ስምምነት መፈራረማቸውን ነው።

እጅግ ታሪካዊ በተባለው በዚህ ስምምነት ፣ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሁለቱ ሀገራት በፀጥታ እና ሰላም ጉዳዮች በሚቻለው ሁሉ ለመተባበር በጋራ መቆም አለባቸው ብለዋል።

ዩክሬን ለረዥም ጊዜ የሚሆን ወታደራዊ አቅሟን ፍፁም አስተማማኝ በሆነ መንገድ ማጠናከር አለባት ሲሉም ማክሮን አክለዋል ።

ሁለቱ ሀገራት የጦር መሳሪያ ስምምነት እያደረጉ ባሉበት ሰዓት የሩሲያ ሀይሎች ወደ ምስራቅ ዩክሬን እየገሰገሱ መሆናቸው ታውቋል።

ኡፒ፣ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ እና ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግበውታል ።

በ-ቶማይ መኮንን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...