በህንድ አምባሳደር አኒል ኩማር የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኘ

Date:

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ለአምባሳደሩ እና ልዑካቸው በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የቴክኖሎጂ ስራዎች ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡

ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሁለቱ ሀገራት በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ላይ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪይ ውይይት አድርገዋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ እየሰራቸው የሚገኙ ስራዎች በአፍሪካ በኤ.አይ ቴክኖሎጂ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የያዘውን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን አምባሳደሩ ገልጸዋል፡፡

አምባሳደሩ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በቴክኖሎጂው ዘርፍ ለማጠናከር በሀገራቱ መሪዎች መካከል ውይይቶች ሲደረጉ መቆየታቸውን አስታውሰው ሀገራቸው በሰው ኃይል አቅም ግንባታ ኢትዮጵያን ለመደገፍ በትኩረት እንደምትሰራበት አጽንኦት ሰተዋል፡፡

ልዑካኑ በኢንስቲትዩቱ የሚገኙትን የሮቦቲክስ ዎርክሾፕ፣ ሾውሩም እንዲሁም የስታርታፕ ማዕከል እና ዩኒፖድን በጉብኝታቸው ወቅት ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...