ከ150 ዓመታት በፊት በመቅደላ ጦርነት ወቅት በእንግሊዝ ወታደሮች ተዘርፎ ከሀገር የወጣውና የዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ባለቤት የእቴጌ ጥሩወርቅ ውቤ ንብረት የሆነው ታሪካዊ የወርቅ የፀጉር ጌጥ በይፋ ለኢትዮጵያ ተመልሷል።
መጋቢት 7 ቀን 2026 እ.ኤ.አ. በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የአሜሪካ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ ሙለን ላይብረሪ በተካሄደ ደማቅ ሥነ-ሥርዓት፣ “ትውስታ፣ ማጣት እና የንጉሣዊ ቅርስ መመለስ” በሚል መሪ ቃል ቅርሱ ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ቀርቧል።
የሮያል ኢትዮጵያ ትረስት መሥራች ልዑል ኤርምያስ ሳህለ ሥላሴ ቅርሱን በይፋ የገለጡ ሲሆን፣ ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱዓለምና የታሪክ ተመራማሪው ዶክተር አሉላ ፓንክረስት ስለ እቴጌዋ ሕይወትና ስለ ቅርሱ ታሪካዊ ፋይዳ ጥልቅ ትንተና ሰጥተዋል።
በ1860ዎቹ አጋማሽ ከመቅደላ ከተዘረፉ በርካታ ቅርሶች አንዱ የሆነው ይህ ጌጥ መመለሱ፣ ወደ ውጭ የተወሰዱ የኢትዮጵያ ቅርሶችን ለማስመለስ ለሚደረገው ብሔራዊ ጥረት ትልቅ ስኬትና መነቃቃት ተደርጎ ተወስዷል።
የሮያል ኢትዮጵያ ትረስት ቅርሱን በማስመለስ ረገድ ላደረገው ከፍተኛ ተጋድሎም በዕለቱ አድናቆት ተችሮታል።
