ሌ/ጄነራል ታደሰ አዲስ አበባ ገቡ !

Date:

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ቀጣይ እጣ ፈንታ ምን ይሆን?

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ፣ በክልሉ ወቅታዊና አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ዛሬ እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ጄነራሉ በቆይታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ከከፍተኛ የፌደራል ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው እንደሚመክሩ የተገለጸ ሲሆን፣ ጉብኝቱ በትግራይ ክልል ባለው የጸጥታና የፖለቲካ ሁኔታ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ምንጮች ጠቁመዋል።

ይህ ጉዞ ትልቅ ትኩረት የሳበው ጄነራል ታደሰ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ተሰጥቷቸው የነበረው የአንድ ዓመት የሥልጣን ጊዜ ከሦስት ቀናት በኋላ (መጋቢት 30) ስለሚያበቃ ነው።

ጄነራሉ ለተጨማሪ ስድስት ወራት በሥልጣን ላይ ይቆያሉ ወይስ አዲስ ምትክ ይመደባል የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል። የአዲስ አበባው ውይይትም የጊዜያዊ አስተዳደሩን ቀጣይ እጣ ፈንታና የክልሉን የሽግግር ሂደት የሚወስን ወሳኝ ክስተት እንደሚሆን ይጠበቃል።

አውራምባ ታይምስ –

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...